ምዕራፍ ፲፮
እግዚአብሔር ሰዎችን ከጥፋትና ከውድቀት ሁኔታቸው ያድናል—በስጋ ያሉ ቤዛነት እንደሌለ ሆነው ይቀራሉ—ክርስቶስ መጨረሻ የሌለው ህይወትን ወይንም መጨረሻ የሌለው ኩነኔ ትንሳኤን አመጣው። በ፻፵፰ ም.ዓ. ገደማ።
፩ እናም አሁን እንዲህ ሆነ፣ አቢናዲ እነዚህን ቃላት ከተናገረ በኋላ ክንዱን ዘረጋና አለ፥ ሁሉም የጌታን ሀደህንነት የሚያዩበት ቀን ይመጣል፤ ሁሉም ሀገር፣ ነገድ፣ ቋንቋና ህዝብ ዐይን ለዐይን ይተያያሉ እናም በእግዚአብሔር ፊት ፍርዱ ትክክል እንደሆነ ለይናዘዛሉ።
፪ እና ከእዚያም ኃጢአተኞች ሀይጣላሉ፣ እናም ዋይ እያሉ ለየሚያለቅሱበትና በትካዜ የሚጮሁበት፣ እናም ጥርሳቸውን የሚፋጩበት ምክንያት ይኖራቸዋል፣ ይህም የሚሆነው የጌታን ድምፅ ስለማያዳምጡ ነው፤ ስለዚህ ጌታ አያድናቸውም።
፫ ሀስጋዊና አጋንንታዊ ናቸው፣ እናም ለዲያብሎስ፣ አዎን፣ እንዲሁም ያ የቀደመው እባብ እንዲያውም የመጀመሪያ ወላጆቻችንን ሐያሳተው፤ መየውድቀታቸው መንስኤ የሆነውን፣ ለሰው ዘር በሙሉ ስጋዊነት፣ ስሜታዊነት፣ ዲያብሎሳዊነት፣ መጥፎን ከጥሩ ለይተው ሠበማወቅ ራሳቸውን ለዲያብሎስ የሚያስገዙበት ምክንያት የሆነው በእነርሱ ላይ ኃይል አለውና።
፬ የሰው ዘር ሁሉ ሀጠፍቷል፣ እናም እነሆ፣ እግዚአብሔር ህዝቡን ከጠፋበትና ከውድቀት ባያድነው ኖሮ እስከመጨረሻው በጠፋ ነበር።
፭ ነገር ግን አስታውሱ ሀበስጋዊ ተፈጥሮው የቆየ፣ እናም በኃጢያትና በእግዚአብሔር እያመፀ የተጓዘ፣ ወድቆ ይቀራል እናም ዲያብሎስ ሙሉ ስልጣን በእርሱ ላይ ይኖረዋል። ስለዚህ ለእግዚአብሔር ጠላት ሆኖ፣ እርሱ ለቤዛነት እንዳልተደረገለት ይሆናል፣ እናም ደግሞ ዲያብሎስም የእግዚአብሔር ጠላት ነው።
፮ እናም፣ ስለነገሮች መምጣት ሀእንደመጡ በመናገር፣ እንግዲህ ክርስቶስ ወደ ዓለም ባይመጣ ኖሮ ቤዛ ሊሆን አይችልም ነበር።
፯ እናም ክርስቶስ ከሞት ባይነሳ ኖሮ፣ ወይም መቃብርም ድል እንዳይኖረውና ሞትም ሀመውጊያ እንዳይኖረው፣ የሞትን እስር ባይበጣጥስ ኖሮ፣ ትንሣኤም ሊኖር አይችልም ነበር።
፰ ነገር ግን ሀትንሳኤ አለ፤ ስለዚህ ሞት ድል አይኖረውም፤ እናም ለየሞት መውጊያ በክርስቶስ ተውጧል።
፱ እርሱ የዓለም ሀብርሃንና ህይወት ነው፤ አዎን፣ መጨረሻ የሌለው፣ ሊጨልም የማይችል ብርሃን፤ አዎን እናም ደግሞ መጨረሻ የሌለው ህይወት፣ እናም ከእንግዲህ ሞት ሊሆን የማይችልበት።
፲ እንዲሁም ይህ የሚሞተው ሀየማይሞተውን ይለብሳል፣ እናም ይህ የሚበሰብሰው የማይበሰብሰውን ይለብሳል፣ እናም መጥፎም ይሁን መልካም እንደስራቸው መሰረት ለእንዲፈረድባቸው በእግዚአብሔር የፍርድ ወንበር ፊት ሐይቆማሉ—
፲፩ መልካም ከሆኑ ሀመጨረሻ ለሌለው ህይወትና ደስታ ትንሳኤ፤ እናም መጥፎ ከሆኑ፣ ኩነኔ ወደሆነው የእርሱ ላደረጋቸው ለዲያብሎስ በመሰጠት ለመጨረሻ ለሌለው የኩነኔ ትንሳኤ—
፲፪ እና በስጋዊ ፍቃዳቸውና ፍላጎታቸው መሰረት በመሄዳቸው፣ እናም ሀየምህረት ክንዶች ወደ እነርሱ ተዘርግተው ሳለ፣ ጌታን በጭራሽ ባለመጥራታቸው፤ የምህረት ክንዶች ወደ እነርሱ ተዘርግተዋልና፣ እነርሱም አልተቀበሉትም፤ ለጥፋታቸው ማስጠንቀቂያ ቢሰጣቸውም እነርሱ ግን ከእነዚህ አልሸሹም፤ እናም ንስሃ እንዲገቡ ታዘው ነበር ነገር ግን ንስሃ አልገቡም።
፲፫ እናም አሁን፣ ልትንቀጠቀጡና፣ ለኃጢአታችሁ ንስሃ ልትገቡ አይገባችሁምን፤ እናም በክርስቶስ ብቻ ልትድኑ እንደምትችሉ አታስታውሱምን?
፲፬ ስለዚህ፣ ሀየሙሴን ህግ የምታስተምሩ ከሆነ፣ ደግሞ የሚመጣው ነገር ጥላ እንደሆነ አስተምሩ—
፲፭ ቤዛነት ሀዘለዓለማዊ አባት በሆነው በጌታ በክርስቶስ እንደሚመጣ አስተምሯቸው። አሜን።