ምዕራፍ ፲፬
ሳሙኤል በምሽት ብርሃን እንደሚሆን እናም አዲስ ኮከብ በክርስቶስ መወለድ እንደሚሆን ተነበየ—ክርስቶስ ሰዎችን ከጊዜያዊው እንዲሁም ከመንፈሳዊው ሞት ያድናቸዋል—የሞቱም ምልክቶች የሶስት ቀን ጨለማ፣ የአለቶች መፈረካከስ፣ እናም ታላቅ የሆነ የምድር መናወጥን ያጠቃልላል። በ፮ ም.ዓ. ገደማ።
፩ እናም እንግዲህ እንዲህ ሆነ ላማናዊው ሀሳሙኤል ሊፃፉ የማይችሉ ከዚህ የበለጡ ታላቅ ነገሮችን ተንብዮአል።
፪ እናም እነሆ እንዲህም አላቸው፥ እነሆ፣ ምልክትን እሰጣችኋለሁ፤ ከዚህ ወዲያ አምስት ዓመት ይመጣል፣ እናም እነሆ፣ ከዚያም በስሙ የሚያምኑትን ሁሉ ሊያድናቸው የእግዚአብሔር ልጅ ይመጣል።
፫ እናም እነሆ ይህንን የምሰጣችሁ በመምጫው ጊዜ ሀለምልክት እንዲሆናችሁ ነው፤ እነሆም ከመምጣቱ አንድ ቀን በፊት ባለው ምሽትም ምንም ዓይነት ጨለማ እስከማይሆን ድረስ በሰማይ ታላቅ ብርሃን ይሆናል፤ ለሰዎችም እንደ ቀን ሆኖ ይታያቸዋል።
፬ ስለዚህ፣ ልክ አንድ ቀን እንደሆነና፣ ምሽት እንደሌለ፣ አንድ ቀንና አንድ ሌሊት እናም አንድ ቀን ይሆናሉ፤ ይህም ለምልክት ይሆናችኋል፤ ምክንያቱም የፀሐይ መውጫዋንና መጥለቂያዋን ታውቃላችሁና፤ ስለዚህ ሁለት ቀንና አንድ ምሽት እንደሚሆን በእርግጥ ታውቃላችሁ፣ ይሁን እንጂ ምሽቱ ጨለማ አይሆንም፤ እናም ይህ ሀእርሱም ከመወለዱ በፊት የሚሆነው ምሽት ይሆናል።
፭ እናም እነሆ ተመልክታችኋት የማታውቋት አዲስ ሀኮከብም ትወጣለች፤ እናም ይህ ለምልክት ይሆናችኋል።
፮ እናም እነሆ፣ ይህ ብቻም አይደለም፤ በሰማይ ብዙ ምልክቶች እንዲሁም አስደናቂ ነገሮች ይሆናሉ።
፯ እናም እንዲህ ይሆናል፥ ሁላችሁም በመሬት ላይ ሀእስከምትወድቁ ትደነቃላችሁ፣ እንዲሁም ትገረማላችሁ።
፰ እናም እንዲህ ይሆናል፥ በእግዚአብሔር ልጅ ሀየሚያምን ዘለዓለማዊ ህይወት ይኖረዋል።
፱ እናም እነሆ፣ ስለነዚህም ነገሮች መጥቼ ለእናንተ እንድናገር ጌታ በመላዕክቱ አዞኛል፤ አዎን እነዚህን ነገሮች ለእናንተ እንድተነብይ አዞኛል፤ አዎን፣ እንዲህም ብሎኛል፥ ንስሃ ግቡ እናም የጌታንም መንገድ አቅኑ ብለህ ለዚህ ህዝብ ጩህ።
፲ እናም እንግዲህ፣ ላማናዊ በመሆኔና ጌታ ያዘዘኝን ቃላት ለእናንተ በመናገሬ፣ እናም ለእናንተ ቃሉም አስቸጋሪ በመሆኑ፣ በእኔ ተቆጣችሁ፣ እናም እኔን ለማጥፋት ፈለጋችሁ፤ ከመካከላችሁም ሀአውጥታችሁ ጥላችሁኛል።
፲፩ እናም ቃላቴን ትሰማላችሁ፤ ምክንያቱም ለዚህ ስል ነው ወደ ከተማዋ ግንብ የመጣሁት፣ ስለዚህ በክፋታችሁም የተነሳ የሚጠብቃችሁን የእግዚአብሔርን ቅጣት ትሰሙት እንዲሁም ታውቁት ዘንድ፤ እናም ደግሞ የንስሃን ሁኔታ እንድታውቁት ዘንድ የመጣሁት፤
፲፪ እናም ደግሞ የእግዚአብሔርን ልጅ፣ የሰማይና የምድር ሀአባት የሆነውን፣ ከመጀመሪያው ጀምሮ የሁሉም ነገሮች ፈጣሪ የሆነውን፣ የኢየሱስ ክርስቶስን መምጣት ታውቁ ዘንድ፤ እናም በስሙም እንድታምኑ ባለኝ አላማ፣ የመምጣቱን ምልክቶች እንድታውቋቸው መጣሁ።
፲፫ እናም በስሙ ሀካመናችሁ፣ ለበመልካምነቱ ለእነዚህ ስርየትን ታገኙ ዘንድ ለኃጢአታችሁ ሁሉ ንስሃን ትገባላችሁ።
፲፬ እናም እነሆ፣ በድጋሚ ሌላ ምልክት እሰጣችኋለሁ፤ አዎን፣ የሞቱን ምልክት።
፲፭ እነሆም፣ ሀደህንነት እንዲመጣ በእርግጥ መሞት ይገባዋል፤ አዎን፣ ሞቱ ሰዎች በጌታ ፊት እንዲቀርቡ የሙታን ለትንሳኤን እንዲያመጣ ጠቃሚ እንዲሁም አስፈላጊ ይሆናል።
፲፮ አዎን፣ እነሆ፣ ይህ ሞት ትንሳኤን ያመጣል፣ እናም የሰው ዘር የሆኑትን በሙሉ ከፊተኛው ሞት ሀያድናል—መንፈሳዊ ከሆነው ሞት፣ የሰው ዘር በሙሉ ለበአዳም መውደቅ ከጌታ ፊት ሐተለይተዋል፣ በጊዜያዊም በመንፈሳዊም መሞት እንደሞቱ ናቸው።
፲፯ ነገር ግን እነሆ፣ የክርስቶስ ትንሣኤ የሰው ዘርን፣ አዎን፣ የሰው ዘርን በሙሉ ሀያድናል፣ እናም ወደ ጌታ ፊትም ያቀርባቸዋል።
፲፰ አዎን፣ እናም የንስሃንም አካሄድ ያመጣል፤ ንስሃ የሚገባ ቢኖር አይቆረጥምና ወደ እሳቱም አይወረወርም፤ ነገር ግን ንስሃ የማይገባ ይቆረጣል፣ እናም ወደ እሳቱ ይወረወራል፤ በድጋሚም መንፈሳዊ ሞት፣ አዎን፣ ሁለተኛ ሞት በእነርሱ ላይ ይመጣል፤ ለፅድቅ ከሆኑትም ነገሮችም በሚመለከት በድጋሚ ይቆረጣሉና።
፲፱ ስለዚህ ንስሃ ግቡ፤ ንስሃ ግቡ፣ እነዚህን ነገሮች በማወቃችሁ፣ እናም ባለማድረጋችሁ ራሳችሁን በእርግማን ስር በማድረግ ታሰቃያላችሁና፤ እናም ወደዚህ ሁለተኛ ሞትም ራሳችሁን ትጎትቱታላችሁ።
፳ ነገር ግን እነሆ፣ ስለሌላው ምልክት፣ የሞቱን ሀምልክት፣ በሚመለከት እንደነገርኳችሁ፤ እነሆ በሚሞትበት በዚያ ቀን፣ ፀሐይ ለትጨልማለች፣ እናም ለእናንተ ብርሃን አትሰጥም፤ ደግሞ ጨረቃና ከዋክብትም ይጨልማሉ፤ እናም ከሞተበት ጊዜም እንኳን ጀምሮ ሐለሶስት ቀናት፣ ከሞት እስከሚነሳበት ጊዜ ድረስ፣ በዚህ በምድር ላይ ምንም ብርሃን አይኖርም።
፳፩ አዎን፣ ነፍሱን አሳልፎ በሚሰጥበት ጊዜ ለብዙ ሰዓታት ሀነጎድጓድ እንዲሁም መብረቅ ይሆናል፣ እናም ምድር ትንቀጠቀጣለችና ትናወጣለች፤ እናም በምድር ላይ ያሉ ዓለቶች፣ በዚህ ጊዜ ጠጣር እንደነበሩ የምታውቋቸው ወይም አብዛኛው ክፍል አንድ ጠጣር የነበሩት፣ ከምድር በላይ የነበሩትና ከሥር ያሉትም ሁሉ ለይሰባበራሉ፤
፳፪ አዎን ሁለት ቦታ ይከፈላሉ፤ እናም ከዚህም በኋላ ተጨማደውና ተሰነጣጥቀው፣ እናም በምድር ላይ የተሰባበሩ ቁርጥራጮች ሆነው፣ አዎን ከመሬት በላይና በታች ሀይገኛሉ።
፳፫ እናም እነሆ፣ ኃይለኛ ነፋስ ይኖራል፣ እናም ከፍታቸው ትልቅ የሆኑ ተራሮች እንደሸለቆ ዝቅ ይላሉ፣ አሁን ሸለቆ ተብለው የሚጠሩትም በከፍታቸውም ትልቅ የሆኑ ተራሮች ይሆናሉ።
፳፬ እናም ብዙ አውራ ጎዳናዎች ይሰባበራሉም፣ ብዙ ሀከተሞችም የወደሙ ይሆናሉ።
፳፭ እናም ብዙ ሀመቃብሮችም ይከፈታሉና ሙታኖቻቸውን አሳልፈው ይሰጣሉ፣ ለብዙ ሰዎችም ብዙ የሆኑ ቅዱሳን ይታዩአቸዋል።
፳፮ እናም እነሆ፣ እንደዚህ ሀመልአኩ ተናግሮኛል፤ ለብዙ ሰዓታትም ነጎድጓድ እንዲሁም መብረቅ እንደሚሆንም ተናግሮኛል።
፳፯ እናም እንዲህ አለኝ፥ ነጎድጓዱና መብረቁ እንዲሁም አይሎ ነፋስ እያለ እነዚህ ነገሮች ይሆናሉ፤ እናም ለሶስት ቀናትም ምድር ሀበጨለማ ትከበባለች።
፳፰ እናም መልአኩ እንዲህ አለኝ፥ ሀእነዚህ ምልክቶች እና እነዚህ ድንቅ የሆኑት በምድር ገፅ ላይ ሁሉ እንደሚሆኑ ያምኑ ዘንድ፣ በሰው ልጆች መካከል የማያምኑበት ምንም ምክንያት እንዳይኖር ከዚህ የበለጡ ታላቅ ነገሮችን ለብዙዎቹ ይታያሉ—
፳፱ እናም ይህም የሚያምን ሁሉ እንዲድን ነው፣ የማያምነውም ጻድቃዊ ሀፍርድ በእርሱ ላይ እንዲመጣ ነው፤ እናም ደግሞ ከተኮነኑ በራሳቸው ላይ የራሳቸውን ፍርድ ያመጣሉ።
፴ እናም አስታውሱ ወንድሞቼ የሚጠፋ ቢኖር የሚጠፋው ለራሱ እንደሆነና፣ ክፋትን የሚሰራም ለራሱ የሚሰራ እንደሆነ ከእንግዲህ አስታውሱ፤ እነሆም፣ እናንተ ሀነፃ ናችሁ፤ ለራሳችሁ እንድትሰሩ ተፈቅዶላችኋል፤ እነሆ እግዚአብሔርም ለእውቀትን ሰጥቷችኋል እናም እናንተን ነፃ አድርጓችኋል።
፴፩ እርሱም መልካምን ከመጥፎ ሀታውቁ ዘንድ እውቀትን ሰጥቷችኋል፤ እናም ለህይወትን አለበለዚያም ሞትን ትመርጡም ዘንድ የነጻ ምርጫ ሰጥቷችኋል፤ እናም መልካምን መስራት ትችላላችሁ፣ መልካም ወደ ሆነውም ሐደግማችሁ ትመለሳላችሁ፣ ወይንም መልካም የሆነው ለእናንተ ይመለስላችኋል፤ ወይም ክፉ መስራት ትችላላችሁ፤ እናም ክፉ የሆነውም ደግሞ ይመለስላችኋል።