ምዕራፍ ፲፫
ሰዎች በታላቁ እምነታቸውና በመልካም ስራዎቻቸው ሊቀ ካህን ተብለው ይጠራሉ—ትዕዛዛቱን ያስተምሩ—በፅድቅ ይቀደሳሉ እናም ወደጌታ እረፍት ይገባሉ—መልከ ጼዴቅ ከእነዚህ ውስጥ አንዱ ነበር—መላዕክት የምስራች ወሬውን በምድሪቱ ያውጃሉ—የክርስቶስን በእርግጥ መምጣቱን ያውጃሉ። በ፹፪ ም.ዓ. ገደማ።
፩ እናም በድጋሚ፣ ወንድሞቼ፣ ጌታ እግዚአብሔር እነዚህን ትዕዛዛት ለልጆቹ ወደሰጠበት ጊዜ አዕምሮአችሁን እጠቁማለሁ፤ እናም ጌታ እግዚአብሔር እነዚህን ነገሮች ለህዝብ እንዲያስተምሩ የልጁ ቅዱስ ሥርዓት መሰረት በሆነው በቅዱስ ሥርዓቱ ካህናትን ሀመሾሙን እንድታስታውሱ እፈልጋለሁ።
፪ እናም ካህናቱ የተሾሙት ሀበልጁ ሥርዓት መሠረት ነበር፣ ለበስርዓቱም ህዝቡ ወልድን ለቤዛቸው በምን ሁኔታ መመልከት እንዳለባቸው ያውቁ ዘንድ ነው።
፫ እናም የተሾሙበት ሥርዓት በዚህ ሁኔታ ነበር—እናም ከዓለም ሀመፈጠር ጀምሮ በእግዚአብሔር ለበቀደመው እውቀት መሰረት በእምነታቸውና በመልካም ስራዎቻቸው ሐተጠርተዋል፣ መተዘጋጅተዋልም፤ በመጀመሪያ ደረጃ መጥፎና ጥሩውን ሠእንዲመርጡ ተትተዋል፤ ስለዚህ መልካሙን በመምረጣቸውና ታላቅ ረእምነትን በመለማመዳቸው በቅዱሱ አጠራር፣ አዎን፣ ለእንደእነዚህ አይነት ሰዎች በቤዛነት ዝግጅት ጋር፣ እናም መሰረት፣ በተዘጋጀው ቅዱስ ጥሪ ሰተጠርተዋል።
፬ እናም በእምነታቸው የተነሳ ለዚህ ቅዱሱ ጥሪ እንደዚህም ሀተጠርተዋል፣ ይህ ሆኖ ሳለ፣ ሌሎች በልባቸው ጠጣርነትና በአዕምሮአቸው መታወር የእግዚአብሔርን መንፈስ አይቀበሉ፣ በሌላ መልኩ፣ በዚህ ባይሆን ኖሮ እንደወንድሞቻቸው ታላቅ ለመብት ይኖራቸው ነበር።
፭ በአጠቃላይ በመጀመሪያ ደረጃ እነርሱ ከወንድሞቻቸው ጋር ሀአንድ ዓይነት አቋም ነበራቸው፣ ይህ ቅዱሱ ጥሪም ከዓለም መፈጠር ጀምሮ ልባቸውን ላላጠጠሩት ተዘጋጅቷል፣ የተዘጋጀውም በአንድያ ልጁ የኃጢያት ክፍያ አማካኝነት በኩል እና ውስጥ ነበር—
፮ እናም በቅዱሱ ጥሪው እንዲህ በመጠራትና፣ ወደ ሀእረፍቱም ይገቡ ዘንድ ለሰው ልጆች ትዕዛዛቱን ለማስተማር በእግዚአብሔር ቅዱሱ ስርዓት መሠረት ወደ ታላቁ ክህነት ተሹመዋል—
፯ ይህም ታላቁ ክህነት ከአለም መፈጠር ጀምሮ ከነበረው ከወልድ ሥርዓት መሰረት ነው፤ ወይም በሌላ አነጋገር፣ ሀመጀመሪያም ቀናት ሆነ ፍፃሜ አመታት የሌለው፤ ለሁሉም ነገር ለበቀደመው እውቀቱ መሰረት ከዘለዓለም እስከዘለዓለም የተዘጋጀ ነው—
፰ አሁን በእንደዚህ ዓይነት ሁኔታ ሀተሹመዋል—በቅዱሱ ጥሪም ተጠርተውና፣ በቅዱሱ ስርዓት ተሹመው፣ ጥሪውና፣ ሹመቱ፣ እና ታላቁ ክህነት መጀመሪያና መጨረሻ የሌለውን የቅዱሱን ስርዓት ታላቅ ክህነት ተቀብለዋል—
፱ መጀመሪያ ቀናት ሆነ መጨረሻ አመታት በሌለው፣ ሀበፀጋ፣ ፍትህና እውነት በተሞላው በአብ አንድያ ልጅ፣ እንደ ወልድ ስርዓት መሠረት ለዘለአለም ለሊቀ ካህናት እንደዚህ ሆኑ። እናም እንደዚህ ነው። አሜን።
፲ እንግዲህ፣ ስለቅዱሱ ስርዓትም ሆነ ስለዚህ ሀታላቁ ክህነት በተመለከተ በተናገርኩ ጊዜ፣ ብዙዎች የተሾሙና የአምላክ ሊቀ ካህን የሆኑ ነበሩ፤ እናም ይህም በታላቁ እምነታቸውና ለንስሃ በመግባታቸው፣ እናም በእግዚአብሔር ፊት ባላቸው ብፁዕነት ንስሃ ለመግባትና ከመጥፋትም ፅድቅን ለመስራት በመምረጣቸው ምክንያት ነው፤
፲፩ ስለዚህ በዚህ ቅዱስ ስርዓት ተጠርተው ነበር፣ ሀተቀድሰውም ነበር፣ እናም በበጉ ደም ለልብሳቸው እስከሚነጣ ታጥበው ነበር።
፲፪ እንግዲህ እነርሱ ሀበቅዱስ መንፈስ ለከተቀደሱ በኋላ፣ ልብሳቸው ከነጣ፣ በአምላክ ፊት ሐንፁህና እንከን የለሽ ከሆኑ፣ መኃጢያትን ሠከመጥላት በቀር ሊመለከቱትም አልቻሉም፣ እናም ንፁህ የሆኑና ወደጌታ አምላካቸው እረፍት የገቡ ብዙዎች፣ እጅግ ብዙዎች፣ ነበሩ።
፲፫ እናም አሁን፣ ወንድሞቼ፣ በእግዚአብሔር ፊት ራሳችሁን ትሁት እንድታደርጉ፣ እናም ለንስሃም ብቁ የሆነ ሀፍሬን እንድታመጡ፣ እናንተም በእረፍቱ ትገቡ ዘንድ እፈልጋለሁ።
፲፬ አዎን፣ እኔ በተናገርኩት ተመሳስይ ሥርዓት መሠረት ሊቀ ካህን የነበረው፤ ታላቁ ክህነትን ለዘለአለም እንደተቀበለው ሀመልከ ፄዴቅ ጊዜ እንደነበሩት ሰዎች ራሳችሁን ትሁት አድርጉ።
፲፭ እናም ለዚህ መልከ ፄዴቅ ነበር ሀአብርሃም ለአስራት የከፈለው፣ አዎን፣ አባታችን አብርሃም ከነበረው ሀብት እንኳን አንድ አስረኛውን አስራት ከፍሏል።
፲፮ አሁን ይህ የሥርዓቱም ሁኔታ ሆኖ ወይንም ይህ የእርሱ ሀሥርዓት ሆኖ፣ በዚህ ህዝብ ወደ እግዚአብሔር ልጅ ይመለከቱ ዘንድ እነዚህ ስርዓቶች ለበዚህ ሁኔታ ነበር የተሰጡት፣ እና ይህም ለኃጢአታቸው ሥርየትም ወደፊት ወደእርሱ ይመለከቱት ዘንድ፣ ወደጌታም ዕረፍት ይገቡበት ዘንድ ነው።
፲፯ እንግዲህ ይህ መልከ ፄዴቅ በሳሌም ምድር ንጉስ ነበር፣ እናም ህዝቡም በክፋትና በእርኩሰታቸው የጠነከሩ ነበሩ፤ አዎን፣ ሁሉም የተሳሳቱ ነበሩ፤ በሁሉም ዓይነት ክፋትም ተሞልተው ነበር።
፲፰ ነገር ግን መልከ ፄዴቅ ታላቅ እምነትን ተለማመደ፣ የታላቅ ክህነት ሀላፊነትን በእግዚአብሔር ሀቅዱሱ ስርዓት መሰረት በመቀበል ለህዝቡ ንስሃን ሰበከ። እናም እነሆ፣ እነርሱ ንስሃ ገቡ፤ በዘመኑም መልከ ጼዴቅ ሰላምን በምድር ውስጥ መሰረተ፤ ስለዚህ የሳሌም ንጉስ በመሆኑ የሰላም አለቃ ተብሎ ተጠርቷል፤ እናም በአባቱም በታች ነገሰ።
፲፱ አሁን፣ ከፊቱ ሀብዙዎች ነበሩ፣ እናም ደግሞ ከእርሱ በኋላ ደግሞ ብዙዎች ነበሩ፣ ነገር ግን ለማንም ታላቅ አልነበረም፤ ስለዚህ፣ በይበልጥ ስለእርሱ በልዩ ጠቅሰዋል።
፳ አሁን ይህን ጉዳይ እንደገና መናገር አያስፈልገኝም፣ የተናገርኩት ይበቃል። እነሆ፣ ሀቅዱሳት መጻሕፍት ከፊታችሁ ይገኛሉ፤ ለየምታጣምሙት ከሆነ ለጥፋታችሁ ይሆናል።
፳፩ እናም አሁን እንዲህ ሆነ አልማ እነዚህን ቃላት ለእነርሱ በተናገረ ጊዜ፣ እጁን ዘርግቶ በኃይል እንዲህ በማለት ይጮህ ነበር፥ አሁን ሀየንስሃ ጊዜ ነው፣ የደህንነት ቀን ቀርባለችና፤
፳፪ አዎን፣ እናም የጌታ ድምፅ፣ በመልአኩ ሀአንደበት፣ ለሀገር ሁሉ አውጇል፣ አዎን፣ በታላቅ ደስታ የምስራች ወሬ ይኖራቸው ዘንድ ያውጀዋል፤ አዎን፣ እናም በህዝቡ መካከል፣ አዎን፣ በምድር ፊት እስከዳርቻ ለተበተኑትም እንኳን፣ እነዚህን የምስራች እንዲሰሙ ያደርጋል፤ ስለዚህ እነዚህ ወደእኛ መጥተዋል።
፳፫ እናም እኛ እንድንረዳቸው ዘንድ፣ እንዳንሳሳት ዘንድ፣ ሀበግልፅ አባባል እንድናውቃቸው ተደርገዋል፤ እናም ይህም የሆነው በባዕድ ምድር ለበመዘዋወራችን ነው፤ ስለዚህ፣ እኛ እነዚህን የምስራች ወሬዎች በወይን አትክልት ቦታዎቻችን ሁሉ ስለታወጁልን በይበልጥ ሞገስን አግኝተናል።
፳፬ እነሆም፣ ሀመላዕክት በዚህ ጊዜ በምድራችን ላይ ለብዙዎች እያወጁ ናቸው፤ እናም የዚህም ዓላማ በክብሩ ለሚመጣበት ጊዜ የሰው ልጆችን ልብ ለማዘጋጀት ነው።
፳፭ እናም አሁን ስለእርሱ መምጣት በመላዕክት አንደበት የሚነገሩትን አስደሳች ዜና ለማዳመጥ ብቻ እየጠበቅን ነን፤ ጊዜው እየመጣ ነው፣ እንዴት እንደፈጠነ ሀአናውቅም። በእኔ ቀናት እንዲሆን ዘንድ እግዚአብሔር ይፍቀደው፤ ነገር ግን በፍጥነት ወይም ዘግይቶ ቢሆን ይሁን፣ በእዚህም እደሰታለሁ።
፳፮ እናም ይህ በመልአኩ አንደበት፣ በሚመጣበት ጊዜ፣ እርሱን በተመለከተ በውስጣቸው በነበረው የትንቢት መንፈስ መሰረት የተናገሩት የአባቶቻቸው ቃላት እንደሚሟሉ ሀለእውነተኛና ለቅዱሳን ሰዎች እንዲታወቅ ይደረጋል።
፳፯ እናም አሁን፣ ወንድሞቼ፣ ከልቤ ውስጣዊ ቦታ፣ አዎን እስከህመም በሚሆን በታላቅ ጭንቀት፣ ቃሌን ታደምጡኝ ዘንድ፣ እናም ኃጢአታችሁን ታስወግዱና፣ የንስሃችሁን ጊዜ እንዳታዘገዩት ሀእመኛለሁ፤
፳፰ ነገር ግን በጌታ ፊት ራሳችሁን ትሁት ታደርጉ ዘንድና፣ ቅዱስ ስሙን ትጠሩ ዘንድ፣ እናም ያለማቋረጥ ሀእንድትተጉ እንዲሁም እንድትፀልዩ፣ ከሚቻላችሁ በላይም ለእንዳትፈተኑም፣ እናም ትሁት፣ ሐየዋህ፣ ታዛዥ፣ ታጋሽ፣ ፍቅር የሞላባችሁና ፅኑ መከራን ቻይ በመሆን በመንፈስ ቅዱስ የምትመሩ እንድትሆኑ እመኛለሁ።
፳፱ ሀበጌታ እምነት ይኑራችሁ፣ ዘለአለማዊ ህይወትን ለመቀበል በተስፋ የተሞላችሁ ሁኑ፣ በመጨረሻው ቀን ከፍ እንድትሉና ለወደእረፍቱም እንድትገቡ፣ ሐየእግዚአብሔር ፍቅር ሁልጊዜም በልባችሁ ይሁን።
፴ እናም ቁጣውን በላያችሁ ላይ እንዳታመጡ፣ ሀበሲኦል ሰንሰለትም እንዳትታሰሩ፣ በሁለተኛ ለሞትም እንዳትሰቃዩ፣ ጌታ ንስሃን ይስጣችሁ።
፴፩ እናም አልማ በዚህ መፅሐፍ ያልተፃፉ ከዚህ የበለጡትን ብዙ ቃላት ለህዝቡ ተናገረ።