መፅሐፈ አልማ
የአልማ ልጅ
የአልማ ልጅ፣ በኔፊ ህዝብ ላይ የመጀመሪያውና ዋናው ዳኛ፣ እናም ደግሞ የቤተክርስቲያኗ ሊቀ ካህን የሆነው፣ የአልማ ታሪክ። የመሣፍንት የንግስ፣ እናም በህዝቡ መካከል የነበረው የጦርነትና ፀብ ታሪክ። እናም ደግሞ የመጀመሪያውና ዋናው ዳኛ በሆነው በአልማ መዝገብ መሰረት በኔፋውያንና በላማናውያን መካከል የነበረው የጦርነት ታሪክ።
ምዕራፍ ፩
ኔሆር ሀሰተኛ ትምህርት አስተማረ፣ ቤተክርስቲያንን አቋቋመ፣ የካህን ተንኮልን ጀመረ፣ እናም ጌዴዎንን ገደለው—ኔሆር የተሰቀለው በወንጀሉ ነው—የካህን ተንኮልና ስደት በህዝቡ መካከል ተስፋፋ—ካህናት ራሳቸውን በራሳቸው ይረዳሉ፣ ህዝቡ ለድሆች እንክብካቤ አደረጉ፣ እናም ቤተክርስቲያኗ በለፀገች። ከ፺፩–፹፰ ም.ዓ. ገደማ።
፩ እናም እንዲህ ሆነ መሳፍንቶች በኔፊ ህዝብ ላይ በነገሱበት በመጀመሪያው ዓመት፣ ንጉስ ሞዛያ በቦታውም ማንም እንዲነግስ ሳያደርግ፣ ሀምድር ሁሉ ወደሚሄዱበት ሄዷል፣ መልካሙን ገድል ተጋድሏል፣ በእግዚአብሔር ፊት በልበ ቅንነት ተራምዷል፤ ይሁን እንጂ ለህግጋትን አቋቁሟል፣ እናም እነርሱም በህዝቡ ዘንድ ተቀባይነትን አግኝተዋል፣ ስለሆነም፣ ከዚህም ጊዜ በኋላ፣ ህዝቡ እርሱ ባቋቋመው ህግጋት ለመገዛት ተገደው ነበር።
፪ እናም እንዲህ ሆነ በአልማ በዳኝነት መቀመጫ ላይ በሚነግስበት በመጀመሪያው ዓመት፣ አንድ ሀሰው እንዲፈረድበት ወደ ፍርድ ወንበሩ አምጥተውት ነበር፤ ሰውየውም ትልቅ የነበረ እና በጥንካሬውም የሚታወቅ ነበር።
፫ እናም ይህ ሰው ከህዝቡ መካከል በመሄድ እርሱ ሀየእግዚአብሔር ቃል ብሎ ያለውን በመስበክ፣ ለየቤተክርስቲያኗ ተቃራኒ በመሆን፣ ለህዝቡም ካህንና መምህር ሁሉ ሐታዋቂ መሆን እንዳለባቸው፣ እናም በእጃቸውም መመስራት እንደሌለባቸው፣ ነገር ግን በህዝቡ መደገፍ እንዳለባቸው ያውጅ ነበር።
፬ እናም ደግሞ ለህዝቡ የሰው ዘር ሁሉ በመጨረሻው ቀን መዳን እንዳለበት፣ እናም መፍራትም ሆነ መንቀጥቀጥ እንደሌለባቸው፣ ነገር ግን ጌታ ሁሉን በመፍጠሩና ደግሞም ሁሉን በማዳኑ እራሳቸውን በማቅናት እንዲደሰቱ፣ እንዲሁም በመጨረሻ ሁሉም ሰው ዘለአለማዊ ህይወት ሊኖረው ይገባል በማለት መሰከረ።
፭ እናም እንዲህ ሆነ እነዚህን ነገሮች በብዛት አስተምሮ ብዙዎች የእርሱን ቃላት አመኑ፣ ይህም ሆኖ ብዙዎች እንኳን እርሱን መደገፍ እናም ገንዘብ ይሰጡት ጀመር።
፮ እናም በልቡ ኩራት መወጠር፣ እናም ውድ ልብስ መልበስ ጀመረ፤ አዎን፣ እናም ከሰበካው ጋር በሚዛመድ ሁኔታ እንኳን ሀቤተክርስቲያንን ማቋቋም ጀመረ።
፯ እናም እንዲህ ሆነ በቃሉ ላመኑት ለመስበክ በመጓዝ ላይ እንዳለ በእግዚአብሔር ቤተክርስቲያን አባል፣ አዎን፣ የእነርሱም መምህር የነበረ፣ አንድን ሰው አገኘ፤ እናም የቤተክርስቲያኗን ሰዎችም ይለውጣቸው ዘንድ፣ ከእርሱ ጋር በኃይል መከራከር ጀመረ፤ ነገር ግን ሀበእግዚአብሔር ቃል በመገሰፅ ሰውየው ተቃወመው።
፰ የሰውየው ስምም ሀጌዴዎን ነበር፤ እናም የሊምሂን ህዝብ ከባርነት ለማስለቀቅ በእግዚአብሔር እጅ መሳሪያ የነበረው እርሱ ነበር።
፱ አሁን ጌዴዎን በእግዚአብሔር ቃል ስለተቃወመው በጊድዮን ተቆጣ፤ እናም ጎራዴውን መዘዘና ይመታው ጀመረ። እንግዲህ ጌዴዎን በማርጀቱ ምቱን ለመቋቋም አልቻለም ነበር፣ ስለሆነም በጎራዴው ሀሞተ።
፲ እናም ገዳዩ በቤተክርስቲያኗ ሰዎች ተወሰደ፣ እናም በፈፀመው ወንጀል ሀእንዲፈረድበት በአልማ ፊት ቀረበ።
፲፩ እናም እንዲህ ሆነ ከአልማ ፊት ቆመና በታላቅ ድፍረት ለራሱ ተከራከረ።
፲፪ ነገር ግን አልማ እንዲህ ሲል ተናገረው፥ እነሆ በዚህ ህዝብ መካከል የካህን ተንኮል ከተጀመረበት ጊዜ ይህ የመጀመሪያው ነው። እናም እነሆ አንተ ሀበካህን ተንኮል ብቻ አይደለም ጥፋተኛ የሆንከው፣ ነገር ግን ይህን በጎራዴው ለማስገደድ ጥረት አድርገሀል፤ እናም የካህን ተንኮል በህዝቡ መካከል በግዴታ የሚደረግ ቢሆን ይህም አጠቃላይ ጥፋታቸውን ያስከትላል።
፲፫ እናም አንተ የፃድቁን ደም አፍስሰሀል፣ አዎን፣ በዚህ ህዝብ መካከል ብዙ መልካምን ያደረገውን ሰው፤ እናም አንተን እንድትተርፍ ካደረግን የእርሱ ደም ሀለበቀል በእኛ ላይ ይመጣል።
፲፬ ስለሆነም የመጨረሻው ንጉሳችን በሆነው በሞዛያ በተሰጠን ህግ መሰረት እንድትሞት ሀተፈርዶብሀል፤ እናም ህጉ በህዝቡ ተቀባይነት አግኝቶኣል፤ ስለዚህ ህዝቡ በህጉ መተዳደር አለበት።
፲፭ እናም እንዲህ ሆነ እርሱንም ወሰዱት፤ ስሙም ሀኔሆር ነበር፤ እናም ወደ ማንቲ ኮረብታ ጫፍ ወሰዱት፤ እናም በእዚያ ለህዝቡም ያስተማረው ከእግዚአብሔር ቃል ጋር ተቃራኒ እንደነበረ በሰማይና በምድር መካከል ተቀባይ እንዲሆን ተገደደ ወይም ተቀበለ፤ እናም በእዚያም በአሳፋሪ ለሞት ተሰቃየ።
፲፮ ይሁን እንጂ፣ ይህ የካህን ተንኮል በምድሪቱ እንዳይስፋፋ ገደብ አልሆነም፣ ምክንያቱም የዓለምን ከንቱ ነገሮች የሚያፈቅሩ ብዙዎች ነበሩና፣ እናም ሐሰተኛ ትምህርቶችን በመስበክ ሄዱ፤ እናም ይህንን ያደረጉት ሀለሀብትና ለክብራቸው ነበር።
፲፯ ይሁን እንጂ፣ ህጉን በመፍራት ሀለመዋሸት አይደፍሩም ነበር፣ ምክንያቱም ይህ ቢታወቅ ኖሮ ሀሰተኞች ይቀጣሉና፤ ስለሆነም በእምነታቸው እንደሚሰብኩ ያስመስላሉ፤ እናም አሁን ህጉ በማንኛውም ሰው ለእምነት ላይ ስልጣን ሊኖረው አይችልም።
፲፰ እናም ህጉን በመፍራት ሀለመስረቅ አልደፈሩም፤ እንደነዚህ አይነቶች ተቀጥተዋልና፤ ለመዝረፍም ሆነ፣ ለለመግደል አልደፈሩም፣ የገደለ ሐበሞት ይቀጣልና።
፲፱ ነገር ግን እንዲህ ሆነ የእግዚአብሔር ቤተክርስቲያን አባል ያልሆኑት የእግዚአብሔር ቤተክርስቲያን አባል የሆኑትን፣ እናም በራሳቸው ላይ የክርስቶስን ስም የለበሱትን አሳደዱ።
፳ አዎን እነርሱንም አባረሩአቸው፣ እናም በሁሉም ዓይነት ቃላት አሰቃዩአቸው፣ ይህም በትህትናቸው የተነሳ፣ እናም በአመለካከታቸው ኩሩ ስላልነበሩና፣ የእግዚአብሔርን ቃል ሀያለገንዘብና ያለምንም ክፍያ አንዳቸው ለሌላኛው የሚካፈሉ ስለነበሩ ነው።
፳፩ እንግዲህ በቤተክርስቲያኗ አባል የሆነ ማንም ሰው በቤተክርስቲያኗ አባል ያልሆኑትን ተነስቶ የሚያሳድድ መኖር እንደሌለበት፣ እናም በመካከላቸውም ምንም ሀስደት መኖር እንደሌለበት በቤተክርስቲያኗ ሰዎች መካከል ህጉ ጥብቅ ነበር።
፳፪ ይሁን እንጂ፣ ከእነርሱ መካከል ብዙ መኩራት የጀመሩ፣ እናም ከጠላቶቻቸው ጋር፣ እስከመመታታትም ድረስ፣ በኃይል መጣላት የጀመሩ ነብሩ፣ አዎን፣ በቡጢም አንዱ በሌላኛው ይመታታሉ።
፳፫ አሁን ይህ በአልማ ሁለተኛው የንግስ ዓመት ውስጥ ነበር፤ እናም ለቤተክርስቲያኗ ታላቅ ስቃይ ምክንያት ነበር፤ አዎን፣ ለቤተክርስቲያኗ ታላቅ ፈተና ምክንያት ነበር።
፳፬ የብዙዎች ልብ ጠጥሯል፣ እናም ከእንግዲህ በእግዚአብሔር ሰዎች መካከል እንዳይታወሱም ስማቸው ሀተደምሠዋልና። እናም ደግሞ ብዙዎች ራሳቸውን ከመካከላቸው ለአወጡ።
፳፭ አሁን በእምነታቸው ፀንተው ለቆሙ ይህ ታላቅ ችግር ነበር፤ ይሁን እንጂ፣ የእግዚአብሔርን ትዕዛዛት በመጠበቅ ፅኑና የማይነቃነቁ ነበሩ፣ እናም በላያቸው ላይ የተቆለለውን ጭቆና ሀበትዕግስት ተወጡ።
፳፮ እናም ካህናት የእግዚአብሔርን ቃል ለህዝቡ ለመናገር ሀስራቸውን በተዉ ጊዜ፣ ሰዎቹም ቢሆኑ የእግዚአብሔርን ቃል ለማዳመጥ ስራቸውን ትተዋል። እናም ካህናት የእግዚአብሔርን ቃል በተናገሩ ጊዜ በድጋሚ ወደ ስራዎቻቸው በትጋት ተመለሱ፤ እናም ካህኑም፣ እራሱን ከአድማጩ በላይ አላደረገም፣ ምክንያቱም ሰባኪው ከአድማጩ የተሻለ፣ መምህሩም ከተማሪው ምንም የተሻለ አልነበረም፤ እናም ሁሉም እኩል ነበሩና፣ ሁሉም ሰዎች ለበጥንካሬአቸው መሰረት ስራቸውን ይሰራሉ።
፳፯ እናም ማንኛውም ሰው ሀለድሆችና ለችግረኞች፣ እናም ለታመሙና፣ ለተሰቃዩት ባላቸው መጠን ለከቁሳቁሶቻቸው አካፈሉ፤ እናም እነርሱ ውድ ልብሶችን አልለበሱም ነበር፣ ይሁን እንጂ ንፁህና የደስደስ ያላቸው ነበሩ።
፳፰ እና እንደዚህም የቤተክርስቲያን ጉዳዮችን አቋቋሙ፤ እና እንደዚህም ይህ ሁሉ ጭቆና ቢኖርባቸውም የማያቋርጥ ሰላም በድጋሚ ይኖራቸው ጀመር።
፳፱ እናም አሁን፣ በቤተክርስቲያኗ ፅኑነት የተነሳ እጅግ ሀሀብታም መሆን ጀመሩ፣ ሁሉም የሚያስፈልጋቸው ማንኛውም ነገሮች በብዛት ነበራቸው—ብዙ መንጋዎችና ከብቶች፣ ሁሉም ዓይነት ኮርማዎችም፣ ደግሞም ብዙ ጥራጥሬና፣ ወርቅ፣ ብርና፣ የከበሩ ነገሮች፣ እናም ብዙ ለሐርና የተፈተለ ጥሩ በፍታ፣ እናም ሁሉም ዓይነት መልካም ልብሶች ነበሯቸው።
፴ እናም እንዲሁ፣ ሀበብልፅግናቸው ለየተራቁትን ወይም የተራቡትን፣ ወይም የተጠሙት፣ የታመሙትን ወይም ያልተመገቡትን ቢሆን ማንንም አላባረሩም፤ እናም ልባቸውን በሀብት ላይ አላደረጉም፤ ስለዚህ ለሁሉም፣ ለወጣቶችም ሆነ ለሽማግሌዎች፣ ለታሰሩትም ሆነ ነፃ ለሆኑት፣ ለወንድም ሆነ ለሴት፣ ከቤተክርስቲያን ለሆኑም ሆነ ላልሆኑት ደግ ነበሩ፤ በችግር ለነበሩት እንዳደረጉት ሁሉ በሰዎች ፊት ሐአላደሉም።
፴፩ እናም በለፀጉና ከእነርሱ ቤተክርስቲያን ካልሆኑት በበለጠ ሀብታም ሆኑ።
፴፪ ከእነርሱ ቤተክርስቲያን ያልሆኑት ራሳቸውን በጥንቆላና ሀበጣኦት አምላኪነት ወይም ለበስንፍና እናም ሐበከንቱ ልፍለፋ እናም መበቅናትና ክርክር፣ ውድ ልብሶችን በመልበስ፣ በትዕቢት በራሳቸው አይን ሠበመነፋት፣ በማሳደድ፣ በመዋሸት፣ በመስረቅ፣ በመዝረፍ፣ ዝሙትን በመፈፀምና፣ በመግደል፣ እናም ሁሉንም ዓይነት ኃጢያት በመፈፀም ራሳቸውን አስደሰቱ፤ ይሁን እንጂ፣ ህጉ በሚቻለው መጠን በተላለፉት ሁሉ ላይ በኃይል ተደርጓል።
፴፫ እናም እንዲህ ሆነ እንደዚህ ህግን በእነርሱ ላይ በማሳረፍ፣ እያንዳንዱ ሰው በሰራው መሰረት እየተቀጣ፣ እነርሱም ይበልጥ ተረጋጉ፣ እናም የሚታወቅ ከሆነ ምንም ዓይነት ኃጢያት ለመፈፀም አልደፈሩም፤ ስለዚህ፣ እስከ አምስተኛው ዓመት የመሳፍንት አገዛዝ ድረስ በኔፊ ህዝቦች መካከል ከፍተኛ ሰላም ነበር።