ምዕራፍ ፴፩
ኔፊ ክርስቶስ ለምን እንደተጠመቀ ይናገራል—ሰዎች ለመዳን ክርስቶስን መከተል፣ መጠመቅ፣ መንፈስ ቅዱስን መቀበል እናም እስከመጨረሻው መፅናት ይኖርባቸዋል—ንስሀ መግባትና ጥምቀት የጠባቡና ቀጭኑ ጎዳና መግቢያ ናቸው—የዘለዓለም ህይወት ከጥምቀት በኋላ ትዕዛዛትን ለሚጠብቁት ይመጣል። ከ፭፻፶፱–፭፻፵፭ ም.ዓ. ገደማ።
፩ እናም አሁን የተወደዳችሁ ወንድሞቼ፣ እኔ ኔፊ፣ ለእናንተ ሀትንቢት መናገሬን እጨርሳለሁ። እናም በእርግጥ መምጣት አለበት ብዬ ከማውቀው ጥቂት ነገሮችን በስተቀር መፃፍ አልችልም፤ የወንድሜ ያዕቆብንም ጥቂት ቃላት ብቻ ነው መፃፍ የምችለው።
፪ ስለሆነም፣ እኔ የፃፍኳቸው ነገሮች ስለክርስቶስ ሀትምህርት መናገር ካለብኝ በስተቀር ለእኔ በቂ ናቸው፤ ስለሆነም፣ በትንቢቴ ግልፅነት መሰረት በግልፅ እናገራችኋለሁ።
፫ ነፍሴ በግልፅነት ትደሰታለችና፤ ጌታ እግዚአብሔርም በሰዎች ልጆች መካከል የሚሰራው በእንዲህ ያለ ሁኔታ ነውና። ጌታ እግዚአብሔር ለመረዳት ሀብርሃንን ይሰጣልና፤ ለሰዎችም በሚረዱት፣ እንደ ለቋንቋቸው ይናገራቸዋልና።
፬ ስለሆነም፣ እናንተ የተናገርኳችሁ የዓለምን ኃጢያት የሚያስወግደውን የእግዚአብሔርን ሀበግ የሚያጠምቀውን ለነቢይ በተመለከተ ጌታ ያሳየኝን በተመለከተ ያሳየኝን እንድታስታውሱ እፈልጋለሁ።
፭ እናም አሁን የእግዚአብሔር በግ፣ ቅዱስ ሆኖ፣ ፅድቅን ሁሉ ለመፈፀም በውሃ ሀመጠመቅ ካስፈለገው፣ አቤቱ ቅዱስ ያልሆንነው፣ አዎን፣ እኛ በውሃ እንኳን መጠመቅ ምን ያህል ያስፈልገናል!
፮ እናም አሁን፣ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ፣ እጠይቃችኋለሁ—የእግዚአብሔር በግ በውሃ በመጠመቅ ፅድቅን ሁሉ የፈፀመው እንዴት ነበር?
፯ ቅዱስ እንደነበር አታውቁምን? ነገር ግን ቅዱስም እንኳን ቢሆን፣ በስጋ መሰረት ለሰው ልጆች በአብ ፊት እራሱን እንዳዋረደ አሳይቷል፣ እናም ትዕዛዛቱን በመጠበቅ ለእርሱ ሀታዛዥ መሆኑን ለአባቱ መስክሯል።
፰ ስለሆነም፣ እርሱ በውሃ ከተጠመቀ በኋላ መንፈስ ቅዱስ ሀበእርግብ ለአምሳል በላዩ ላይ አረፈ።
፱ እናም እንደገና፣ እርሱ በፊታቸው ምሳሌ በመሆን፣ ለሰዎች ልጆች የጎዳናውን ቀጥተኝነትና፣ እነርሱ በዚያ መግባት ያለባቸው ሀበሩን ጥበት አሳይቷቸዋል።
፲ እናም ለሰዎች ልጆች፣ እኔን ሀተከተሉኝ አለ። ስለዚህ፣ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ የአብን ትዕዛዛት ለመጠበቅ ፈቃደኞች ከመሆን በስተቀር ኢየሱስን ለልንከተለው እንችላለን?
፲፩ እናም አብ እንዲህ ይላል፥ ንስሀ ግቡ፣ ንስሀ ግቡ፣ እናም በተወደደው ልጄ ስም ተጠመቁ።
፲፪ እናም ደግሞ፣ የወልድ ድምፅ ወደ እኔ መጥቶ እንዲህ አለኝ፥ በስሜ የተጠመቀ፣ አብ እንደ እኔ መንፈስ ቅዱስን ሀይሰጠዋል፤ ስለሆነም፣ ለተከተሉኝ፣ እናም እኔ ስሰራ ያያችሁትን ስሩ።
፲፫ ስለዚህ፣ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ፣ በሙሉ ልባችሁ አላማ፣ በእግዚአብሔር ፊት ባለማስመሰልና ያለግብዝነት፣ ነገር ግን በእውነት ፍላጎት፣ ለኃጢአታችሁ ንስሀ በመግባት፣ ሀበጥምቀት የክርስቶስን ስም ለእራሳችሁ መውሰዳችሁን ለአብ በመመስከር ወልድን ብትከተሉ—አዎን፣ እንደቃሉ ጌታችሁንና አዳኛችሁን ወደ ውኃው ብትከተሉ፣ እነሆ፣ ከዚያም መንፈስ ቅዱስን ትቀበላላችሁ፤ አዎን፣ ለየእሳትና የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት ይመጣል፤ እናም ከዚያ በኋላ በመላዕክት ሐልሳን መናገርና ለእስራኤል ቅዱስም በምስጋና መጮህ ትችላላችሁ።
፲፬ ነገር ግን እነሆ፣ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ፣ የወልድ ድምፅ እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፥ ለኃጢአታችሁ ንስሀ ከገባችሁና፣ በውኃ በመጠመቅ ትዕዛዛቴን ለመጠበቅ ፈቃደኛ እንደሆናችሁ ለአብ ከመሰከራችሁ፣ እና የእሳትንና የመንፈስ ቅዱስን ጥምቀት በመቀበላችሁ፣ እናም በአዲስ ልሳን፣ አዎን፣ እንዲያውም በመላዕክት ልሳንም ለመናገር ከቻላችሁ በኋላ፣ ከዚህም በኋላ ሀየምትክዱኝ ከሆነ፣ ፈፅሞ ባታውቁኝ ምንኛ ለይሻላችሁ ነበር።
፲፭ እናም ከአብ እንዲህ የሚል ድምፅ ሰማሁ፥ አዎን፣ የተወደደው ልጄ ቃላት እውነትና የታመኑ ናቸው። እስከመጨረሻው የሚፀና እርሱ ይድናል።
፲፮ እናም አሁን፣ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ፣ የህያው እግዚአብሔርን ልጅ ሀምሳሌን በመከተል ሰው እስከመጨረሻው ለየማይፀና ከሆነ፣ መዳን እንደማይችል በዚህ አውቃለሁ።
፲፯ ስለዚህ፣ ጌታችሁና አዳኛችሁ ሲያደርግ እንዳየሁ የነገርኳችሁን ነገሮች አድርጉ፤ መግቢያችሁን ታውቁት ዘንድ፣ ለዚህም ነው እነዚህን ነገሮች የታዩኝ። የምትገቡበትም በር ንስሀና የውኃ ሀጥምቀት ነው፤ እና ከእዚያም የኃጢአታችሁ ለስርየት በእሳትና በመንፈስ ቅዱስ ይመጣሉ።
፲፰ እና ከእዚያም እናንተ ወደ ዘለዓለማዊው ህይወት በሚመራው በዚህ ሀበቀጭኑና ጠባቡ ለጎዳና ላይ ናችሁ፤ አዎን፣ በበሩ ገብታችኋል፤ በአብና በወልድ ትዕዛዛት መሰረትም አድርጋችኋል፤ እናም በትክክለኛው መንገድ ከገባችሁ ትቀበላላችሁ ያለውን የተስፋውንም ቃል በመፈፀም፣ ስለአብና ስለወልድ ሐየሚመሰክረውን መንፈስ ቅዱስ ተቀብላችኋል።
፲፱ እናም አሁን፣ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ፣ በጠባቡና በቀጭኑ ጎዳና ከገባችሁ በኋላ፣ ሁሉ ሀተደርጓልን? ብዬ እጠይቃችኋለሁ። እነሆ፣ አይደለም፣ እላችኋለሁ፤ በክርስቶስ ቃል በማይናወጥ ለእምነት ለማዳን ኃያል በሆነው መልካም ስራ ሙሉ በሙሉ ሐበመተማመን ባይሆን ኖሮ እስከዚህ አትመጡም ነበር።
፳ ስለሆነም ፍጹም የሆነ ሀየተስፋ ብርሃን፣ እናም የእግዚአብሔርና የሰዎች ሁሉ ለፍቅር እየኖራችሁ በክርስቶስ ባላችሁ ፅኑነት ሐመቀጠል አለባችሁ። ስለሆነም አብም፣ የክርስቶስን ቃል በመመገብ፣ እናም እስከመጨረሻው መበመፅናት የምትቀጥሉ ከሆነ፣ እነሆ አብ እንዲህ ይላል፥ የዘለዓለም ህይወት ይኖራችኋል።
፳፩ እናም አሁን፣ እነሆ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ፣ ሀመንገዱ ይህ ነው፤ ሰው በእግዚአብሔር መንግስት መዳን የሚችልበት ከሰማይ በታች የተሰጠ ሌላ ለምንም መንገድም ሆነ ሐስም የለምና። እናም አሁን፣ እነሆ፣ ይህ የክርስቶስ መትምህርትና፣ መጨረሻ የሌለው ሠአንድ አምላክ፣ ረየአብ፣ የወልድና፣ የመንፈስ ቅዱስ ብቸኛውና እውነተኛው ትምህርት ነው። አሜን።