ምዕራፍ ፲፩
ያዕቆብ መድኃኒቱን አየ—የሙሴ ህግ የክርስቶስ ምሳሌዎች ናቸው እናም የእርሱን መምጣት ያረጋግጣል። ከ፭፻፶፱–፭፻፵፭ ም.ዓ. ገደማ።
፩ እናም አሁን፣ ሀያዕቆብ በዚያን ጊዜ ለህዝቤ ብዙ ነገሮችን ተናገረ፤ ሆኖም እነዚህን ነገሮች ብቻ ለእንዲፃፉ አደረግሁ፣ ምክንያቱም እኔ የፃፍኳቸው ነገሮች ይበቁኛልና።
፪ እናም አሁን እኔ ኔፊ፣ ሀየኢሳይያስን ቃል በተጨማሪ እፅፋለሁ፣ ምክንያቱም በእርሱ ቃል ነፍሴ ትደሰታለች። ቃላቱን ለህዝቤ አመሳስልላቸዋለሁ፣ እናም ለልጆቼ ሁሉ አሰራጫቸዋለሁ፣ ምክንያቱም እርሱ በእውነት ለመድኃኒቴን፣ እኔ እንዳየሁት፣ አይቶታልና።
፫ እናም እኔ እንዳየሁት ወንድሜ ያዕቆብም ደግሞ ሀአይቶታል፤ ስለዚህ፣ ቃሌ እውነት መሆኑን ለማረጋገጥ የእነርሱን ቃል ለልጆቼ እልካለሁ። ስለዚህ፣ እግዚአብሔር ለበሶስት ሰዎች ቃል ቃሌን አፀናለሁ ብሏል። ይሁን እንጂ፣ እግዚአብሔር የበለጡ ምስክሮችን ይልካል፣ እናም ቃሉን በሙሉ ያረጋግጣል።
፬ እነሆ፣ ሀየሚመጣውን ክርስቶስ እውነታ ለህዝቦቼ ለበማረጋገጥ ነፍሴ ትደሰታለች፤ ለዚህም ምክንያት ነው የሙሴ ሐህግ የተሰጠው፤ እናም ከዓለም መጀመሪያ ጀምሮ ለሰዎች በእግዚአብሔር የተሰጡት ነገሮች ሁሉ የእርሱ ምሳሌዎች ናቸው።
፭ እናም ደግሞ ነፍሴ ጌታ ለአባቶቻችን በገባው ሀቃል ኪዳን ትደሰታለች፤ አዎን፣ በፀጋውና በፍርዱና፤ በሀይሉ እና በምህረቱ፣ በታላቁና ከሞት በሚያድነው ዘለአለማዊው እቅዱ፣ ነፍሴ ትደሰታለች።
፮ እናም ክርስቶስ ካልመጣ ሀበስተቀር ሁሉም ሰው እንደሚጠፋ ለህዝቤ በማረጋገጤ ነፍሴ ትደሰታለች።
፯ ክርስቶስ ሀከሌለ እግዚአብሔር አይኖርምና፤ እናም እግዚአብሔር ከሌለ እኛም አንኖርም፣ ምክንያቱም ምንም ፍጡር ለሊኖር አይችልምና። ነገር ግን እግዚአብሔር አለ፣ እርሱም ክርስቶስ ነው፣ እናም በዘመኑ ፍፃሜ ይመጣል።
፰ እናም አሁን ከህዝቤ ማንም ይህንን ቃል የሚያይ ልብን ከፍ እንዲያደርጉና ለሰዎች ሁሉ ይደሰቱ ዘንድ፣ ከኢሳይያስ ቃል በጥቂቱ እፅፋለሁ። አሁን ቃሉ ይህ ነው፣ እናም በራሳችሁና በሁሉም ሰዎች አነፃፅሯቸው።